1. ይዘት
  2. ቀዘፋ
  3. ተጨማሪ ይዘቶች
  4. አብሮ መቅዘፍ
  5. ፍለጋ
  6. ከ 30 ቋንቋዎች ይምረጡ።


 

 | 11.03.2010 | 15:00 UTC

ጀርመን፤ የትምሕርት ቤት ግድያ ታሰበ

በጀርመን ባደን-ቩርተንበርግ ክፍለ-ሐገር መንደር በቪነንደን አልበርትቪል ትምሕርት ቤት ውስጥ አሰቃቂ ግድያ የተካሄደበት አንደኛ ዓመት ዛሬ ታስቦ ዋለ። 900  ገደማ የሚጠጉ ተማሪዎች፣ መምሕራንና የሰለቦቹ ቀሪ ቤተሰብ ዓባላት ከትምሕርት ቤቱ ፊትለፊት በሚገኝ አዳራሽ ውስጥ ተሰብስበው ዕለቱን በሃዘን አስታውሰዋል። ከአንድ ዓመት በፊት በዛሬዋ ዕለት አንድ የ 17  ዓመት ወጣት ተማሪ ተኩስ ከፍቶ ዘጠኝ መሰሎቹንና ሶሥት መምሕራንን መግደሉ ይታወሣል። ወጣቱ በሽሽት ላይ እንዳለ ተጨማሪ ሶሥት ሰዎችን ገድሎ የራሱን ሕይወት ማሳለፉም አይዘነጋም። የትምሕርት ቤቱ አስተዳዳሪ አስትሪድ ሃን እንዳስረዱት ግድያው ያስከተለው የመንፈስ ስቃይ ዛሬም ለብዙ መምሕራን ፈታኝ እንደሆነ ነው። የቪነንደን አብያተ-ክርስቲያን ዛሬ ጧት ላይ ደወል በመደወል ተኩሱ የተከፈተበትን ሰዓት ሲያስቡ ይህንኑ ተከትሎም የአገሪቱ ፕሬዚደንት ሆርስት ኮህለር በተገኙበት ይፋ የሃዘን ስነ-ስርዓት ተካሂዷል። ኮህለር በስነ-ስርዓቱ ላይ ባሰሙት ንግግር የአገሪቱ የመሣሪያ ባለቤትነት ሕግ እንዲጠብቅ ጥሪ አድርገዋል። 



 

DW-TV EUROPE live

Journal

We're sorry, due to legal issues this content can not be transmitted as live stream.

If you are inside the United States, it is still possible for you to enjoy DW-TV. For more information, please click here.

ኢትዮጵያ -ምርጫ 2002
የምርጫ ዘመቻዉ አአ

Audio on Demand

በማድመጥ መማር
በማድመጥ መማር

ማህበራዊ የመረብ ግንኙነት

ትዊተር